ONE LORD,ONE FAITH,ONE BAPTISM,

ONE GOD AND FATHER OF ALL,WHO IS ABOVE ALL,AND THROUGH ALL,AND IN YOU ALL. EPHESIANS.4:5-6

Monday, February 24, 2014

To the Ethiopian Orthodox Church, Lent fasting season means a period of fasting when the faithful undergo a rigorous schedule of prayers and penitence. This fast is observed with greater rigor than any other fast and it is a test of one's Christianity. One who fails to keep it is not considered a good Christian. Properly observed it nullifies the sins committed during the rest of the year. The faithful should abstain from all meat and milk products except bread, water and salt. It consists of 55 days. On all the fasting days only one meal is allowed and this is to be taken in the afternoon, at 3 P.M.. or in the evening. On Saturdays and Sundays people are allowed to eat in the morning. Daily Services are conducted in all the Churches. Each day services are held from morning to 2:45 P.M.. Priests regularly attend night services starting at midnight up to seven A.M. Each week of the Great Lent has its own name associated with what Christ did or taught. The names of the weeks during lent are the following: Name of the weeks 1st zewerede 2nd qidist 3rd mikurab 4th metsagu 5th debrezeit 6th gebrihar 7th nikodimos 8th hosaana 9th Tinsae/Easter Nice lent.

Thursday, May 24, 2012

ጾ መ ሐ ዋ ር ያ ት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን። ጾም ማለት ከምግብና ከመጠጥ ራስን በማቀብ በአንቃዕዶ ልቦና በሰቂለ ኅሊና ሆነን ወደ ፈጣሪ የምንቀርብበትና ለሰራነው ኃጥያት ይቅርታን ፣ለመጣብን ቁጣ ምህረትን፣ለደረሰብን ሕመም ፈውስን ከፈጣሪ ዘንድ የምናገኝበት የእምነት መገለጫ መንገድ ነው። ጾምን ያዘዘው እግዚአብሔር ሲሆን ስርአቱም የተሰራው በአዳምና በሔዋን ዘመን ነው።ከዛም በአበውና በነብያት ሲፈጸም የኖረና በራሱ በእግዚአብሔር ወልድ የጸና ሥርዐት ነው። አዳምና ሔዋን ገና በገነት ሳሉ እግዚአብሔር አምላክ ይህንን ብሉ ይህንን እንዳትበሉ ብሎ የሚበላና የማይበላውን ወይንም የሚጾመውንና የማይጾመውን ምን እንደሆነ አዟቸዋል።ዘፍ. ፪፥፲፯ “ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካምንና ክፉውን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህ። ’’ ይህን በእግዚአብሔር የተሠራ ሥርዓት በማፍረሳቸው አዳምና ሔዋን ተቀጥተዋል።ከገነት ተባረሩ በመጾም ይገኝ ከነበረው ጸጋና በረከት ተለዩ።ይህን ታሪክ የሚያውቁ አባቶቻችን ቅዱሳን ሐዋርያት ወደተጠሩበት ወንጌልን ለዓለም የማዳረስ ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት እግዚአብሔር መጀመሪያ ለሰው የሰጠውን ትእዛዝ ራሳቸው ፈጽመው ሌሎችም ይፈጽሙት ዘንድ ለማስተማርና አገልግሎታቸውም የሰመረ ይሆን ዘንድ አገልግሎታቸውን በጾም ጀምረዋል። ጾም ሰዎች ከእግዚአብሔር ጋር የሚነጋገሩበት እግዚአብሔርን የሚያዩበት መሳሪያ ነው።ሊቀ ነብያት ቅዱስ ሙሴ በሲና ተራራ ከእግዚአብሔር ጋር የተነጋገረውና የአምላኩን ፊት ሊያይ የበቃው ፵ ቀንና ሌሊት ራሱን በጾም ወስኖ ነው። የእግዚአብሔር ማደሪያ የቃል ኪዳኑን ታቦትም ከእግዚአብሔር እጅ ለመቀበል በቃ።ዘዳ. ፱፥፱። የሐዲስ ኪዳን ደቀመዛሙርትም ሐዋርያት ከእግዚአብሔር ጸጋና ኃይል ይሰጣቸው ይበዛላቸው ዘንድ በጾምና በጸሎት ወደ እርሱ ቀርበዋል። “…እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ አለ።በዚያን ጊዜ ከጦሙ ከጸለዩም እጃቸውንም ከጫኑ በኋላ አሰናበቱአቸው።’’ ሐዋ.፲፫፥፪-፫ ። እኛም ይህን የበረከት ጾም ጾመን በረድኤት እንድንኖር አምላከ ሐዋርያት ይርዳን። አሜን!

Saturday, May 19, 2012

ቅዱስያ ያሬድ የደረሳቸው መጽሐፍት፦ - ፩. ድጓ፦ ድጓ የቤተክርስቲያን ዜማ መድብል ሲሆን ዐራት ክፍሎች አሉት እነዚህም በአራቱ የአመት ዘመናት/seasons/ ማለትም በመጸው፣በሃጋይ/በጋ/፣በፀደይና በክረምት ይመደባሉ። አራቱ ክፍሎችም፦ - ሀ - ድጓ ዮሐንስ፦ ስለቅዱስሐንስ መጥምቅ የሚናገር/የሚዘመር ነው። ከመስከረም ፩ እሰከ ኅዳር ፴ ድረስ የሚዘመሩ መዝሙራትን ይዟል። - ለ - ድጓ አስተምሕሮ፦ አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረውን ትምህርት ያደረገውን ተአምራት የያዘ ነው። የሚዘመርበትም ወቅት ከታኅሣስ ፩ እስከ መጋቢት ፴ ባለው ወቅት ነው። - ሐ - ጾመ ድጓ፦ ራሱን የቻለ መጽሐፍ ተደርጎ የሚቆጠር ሲሆን በተለይ በአብይ ጾም የሚዘመሩ መዝሙራትን የያዘ ነው። - መ- ድጓ ዘፋሲካ፦ ከትንሳኤ እሰከ ጷግሜን ባለው ጊዜ ውስጥ የሚዘመሩ መዝሙራትን ያካተተ ሲሆን ሰለ ጌታ የማዳን ሥራ፣ ስለእርገቱ፣ስለመንፈስ ቅዱስና ስለክረምት የሚያወሳ ነው። - ፪. ጾመ ድጓ፡- በአብይ ጾም የሚዘመሩ መዝሙራትን የያዘና ስምንት ክፍሎች ያሉት ነው። እነርሱም የሚከተሉት ናቸው። - ሀ-ዘወረደ ለ-ቅድስት ሐ-ምኩራብ መ-መጻጉ ሠ-ደብረዘይት ረ-ገብርሔር ሰ-ኒቆዲሞስ ሸ-ሆሳዐና - ፫. ዝማሬ፦ በህብረት/በማህበር የሚደርስ ጸሎት/መዝሙር የያዘ ነው። ከቁርባን በኋላ የሚባል ነው። ዝማሬ በአምሰት ይከፈላል፦ ሀ-ህብስት ለ-ጽዋዕ ሐ-መንፈስ መ-ምስጢር ሠ-አኮቴት ይባላሉ - ፬. መዋስዕት፦ ስለጌታችን ጥምቀት፣ትንሳኤና እርገት፣ስለእመቤታችን አማላጅነት፣ስለቅዱሳን ክብርና አማላጅነት የሚዘሩ መዝሙራትን ያካተተ ነው። የሚዘመረውም ለሙታን መታሰቢያ፣ለሆሳዕና እና ለቅዳሜ ስዑር ነው። ቅዱስ ያሬድ ዝማሬ ከተሰኘው ድርሰቱ ጋር የደረሰውና ከዝማሬ ጋር በአንድ ወንበር የሚሰጥ በመሆኑ ዝማሬ መስዋዕት በመባል ይታወቃል። - ፭. ምዕራፍ፦ የዜማ ስብሐተ ነግህ፣መወድስና ክስተት የተባሉትን የመዝሙር አይነቶች ያጠቃልላል። በተጨማሪም የዘወትር የዓመቱን ሳይጠብቅ በዓመት በበአላትና ሳምንታት የሚባል ነው። የዜማዎችን አይነትና ማረፊያዎች ከፋፍሎ የሚነግረን ክፍል ነው። በውስጡ የዜማ ተማሪዎች የሚማሯቸውን ትምህርቶች ይዟል። እነዚህም፦ ውዳሴ ማርያም፣ መስተጋብዕ፣አርባዕት መለኮት፣አርያም፣ክስተትና መወድስ ይባላሉ።

Wednesday, April 11, 2012

‹‹ሰሙነ ሕማማት››
‹‹ሰሙነ ሕማማት›› መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው፡፡ በርካታ ሰዎች ቤተ ክርስቲያንን ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ የምትጓዝ አካል አድርገው ሊገልጧት ይሞክራሉ፡፡ ይህ እጅግ አላዋቂ መሆናቸውን ይመሰክራል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከመጽሐፍ ቅዱስ ያልተገኘና በሥጋዊና በደማዊ እውቀት ላይ የተመሠረተ ሥርዓት የላትም፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ሥራ ‹‹ከሕማማቱ በኋላ›› በማለት ስለ ሰሙነ ሕማማት የሚያወሳ ቃል ተጠቅሟል፡፡ (የሐዋ1፥3)
ሰሙነ ሕማማት የሁለት ቃላት ጥምር ውጤት ነው፡፡ ‹‹ሰሙን›› የሚለው ቃል ‹‹ሰመነ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ስምንት ቀኖች ወይም ሳምንት ማለት ነው፡፡ ‹‹ሕማማት›› የሚለው ቃልም እንደዚሁ ‹‹ሐመመ›› ወይም ‹‹መ›› ጠብቆ ሲነበብ ይጎረድና ‹‹ሐመ›› ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን መከራዎች ማለት ነው፡፡ ይህ ለብዙ ሲሆን ነው፡፡ ለአንድ ወይም ለነጠላ ሲሆን ደግሞ ‹‹ሕማም›› እንላለን፡፡ እንግዲህ ሁለቱን ቃላት በማናበብ ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ስንል ‹‹የመከራዎች ሳምንት›› ማለታችን ነው፡፡
ሕማማት ስንል ምን ዓይነት ሕማም ወይም ምን ዓይነት መከራ በማን ላይ የሚሉት ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት አለባቸው፡፡ ሰዎች ልዩ ልዩ አደጋ ሲደርስባቸው መከራ አገኛቸው ይባላል፡፡ በሽታ ሲይዛቸውና በደዌ ሲሰቃዩ መከራቸውን አዩ እንላለን፡፡ ያላቸውን ሲያጡና ኪሣራ ሲደርስባቸው ሌላው ቀርቶ ሲርባቸውና ሥራ ሲበዛባቸው እንኳን መከራቸውን አዩ ይባላል፡፡
በሰሙነ ሕማማት የምናስበው የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ ከላይ ለሰው ልጆች ከጠቀስነውና ከተለመደው ዓይነት መከራ ይለያል፡፡ የተለየ ጊዜ ተወስኖለት ሰሙነ ሕማማት፣ ሕማማተ መስቀል፣ ሕማማተ ክርስቶስ ወዘተ እያልን በተለየ መንገድና ሥርዓት የምንገልጽውም ልዩ መከራ ስለሆነ ነው፡፡
ሕማማት የምንለው ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ አይሁድ የተቀበለው የሐሰት ክስ፣ ፍርድ፣ መጎተት፣ መገረፍ፣ መገፈፍ፣ እርግጫ፣ ጥፊ፣ ጡጫ፣ ችንካር በአጠቃላይ በበርካታ ድርሳናት የተገለጠው አይሁድ የፈጸሙበትን ግፍ ሁሉ ነው፡፡ የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መከራ በዓላማው፣ በአፈጻጸሙ፣ በመጠኑ፣ በምክንያቱ በአጠቃላይ በምን መልኩ ከሰው ልጆች መከራ ጋር አይመሳሰልም፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ ወልደ እግዚAብሔር ኢየሱስ ክርስቶስን ‹‹የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፡፡›› ይለዋል፡፡ (ኢሳ፶3፥3) ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ የተቀበለው ስለእኛ ሲል ነው፡፡ በእኛ ላይ መድረስ የነበረበትን መከራ ሁሉ እርሱ ተሸከመልን፡፡ የእኛን ሞት ተቀብሎ የእርሱን ሕይወት ለእኛ ሰጠን፡፡ ይህን ሲያስረዳን ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ሕመማችንንም ተሸክሞአል፡፡›› በማለት ጻፈልን፡፡ (ኢሳ፶3፥4) ኢየሱስ ክርስቶስ መከራን የተቀበለው በፈቃዱ ነው፡፡
ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ መከራን ተቀበለ ማለት ግን ግድሉኝ፣ ቸንክሩኝ አላቸው ማለት አይደለም፡፡ አይሁድ መከራ ሲያደርሱበት እነርሱን መቃወም፣ ማጥፋት፣ ወይም እንዳያገኙት ማድረግ ሲችል መከራን ተቀበለ ማለት ነው፡፡ ይህ ሆኖ ሳለ እርሱ ባልሄደበት መንገድ በየዓመቱ የክርስቶስን ሕማማት ለማሰብ እያሉ ቸንክሩን፣ ግረፉን፣ ስቀሉን የሚሉ ሰዎች በዓለም ዙሪያ ተፈጥረዋል፡፡ ይህም በገዛ ሐሳባቸው የሚመሩና ሥርዓት የሌላቸው መሆናቸውን ከማሳየት በቀር የሚጠቅማቸው ነገር የለም፡፡ ይልቅ በውስጡ ብዙ ኃጢአት፣ የእውቀት ማነሥ፣ ወንጀል የሞላበት አካሄድ ነው፡፡
እርሱ ስለ እኛ የተቀበለውን መከራ እኛ በጾም፣ በጸሎትና በስግደት ማሰብ አያቅተንም፡፡ እንድናስበውም የመጽሐፍ ቅዱስ ትእዛዝ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ መከራውን እንድናስብለት ይፈልጋል፡፡ እርሱ ራሱ አማናዊ ሥጋውንና ደሙን
በሰጠን ጊዜ ‹‹ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት›› ብሎናልና፡፡ ሥጋውና ደሙ በመከራው ጊዜ የተሰጠን ነው፡፡ ስለዚህ በሥጋውና በደሙ መከራውን እናስባለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ሥጋውን በበላችሁ ደሙን በጠጣችሁ ጊዜ እለት እለት ሞቱን ትናገራላችሁ›› ያለን ስለዚህ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃላት አክብራ በመያዝ ዘወትር በቅዳሴዋ ‹‹ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ - አቤቱ ሞትህን እንናገራለን፡፡›› ትላለች፡፡
የጌታችን የመከራው መታሰቢያ እንዲደረግ የመጽሐፍ ቅዱስ ትእዛዝ መሆኑን ከላይ አብራርተናል፡፡ ያ ደግሞ እንዲሁ በዘፈቀደ የሚደረግ አይደለም፡፡ ‹‹ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን›› (1ቆሮ04$፵) ስለተባለ ቤተ ክርስቲያን የጌታችችን ሕማማት የምታስብበት ልዩ ወቅትና ሥርዓት አላት፡፡ ወቅቱ በየዓመቱ ለአንድ ሳምንት ሲሆን ‹‹ሰሙነ ሕማማት›› ይባላል፡፡ ሳምንቱ የሚታወቅበት ልዩ ሥራ ደግሞ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደትና መጻሐፍትን ማንበብ ሲሆን ይህም ‹‹ግብረ ሕማማት›› ይባላል፡፡ ይህን ሥርዓት ለማካሄድ የሚረዳው የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ እንደ ግብሩ ‹‹ግብረ ሕማማት›› ተብሏል፡፡
‹‹እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐኒ ወያብጽሕክሙ እግዚአብሔር በሰላም፡፡›› አሜን!
በዲያቆን ኅብረት የሺጥላ
E-mail - hibretyes@yahoo.com